Saara Mohammed
Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Saara Mohammed, Health/Beauty, Dire, Addis Ababa.
01/07/2026
የብዝሃ ዘርፍ ሪፎርሙ የቱሪዝሙን የኢኮኖሚ አበርክቶ አሳድጓል -ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
የብዝሃ ዘርፍ ሪፎርሙ ለቱሪዝም መስክ የኢኮኖሚ አበርክቶ ማደግ ትልቅ ሚና መጫወቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኤንቢሲ ኢትዮጵያ ጋር ቱሪዝም አዲሱ የኢኮኖሚ ሞተር በሚል ርዕስ ቆይታ አድርገዋል።
መንግስታቸው የጀመረው የብዙሃ-ዘርፍ (Multi-sectoral) የኢኮኖሚ ሪፎርም በአሁኑ ወቅት በአስደናቂ ሁኔታ ውጤት እያስመዘገበ እንደሚገኝም ገልጸዋል።
በግብርናው ዘርፍ በስንዴ፣ በቡና፣ በሩዝ እንዲሁም በፍራፍሬ ልማት የተገኙ ውጤቶች ለሀገር ውስጥ ምርታማነት ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን ጠቁመዋል።
ከዚህም በተጨማሪ እንደ ሌማት ትሩፋት ያሉ ኢኒሼቲቮች፣ የቴክኖሎጂ ሪፎርሞች፣ የመሶብ ፕሮጀክት እና የአምስት ሚሊየን ኮደሮች የስልጠና መርሃ-ግብር ለጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) እድገት የበኩላቸውን ጉልህ ድርሻ እየተወጡ መሆኑን አስገንዝበዋል።
በኢንዱስትሪ እና በማዕድን ዘርፎች የተመዘገቡት ስኬቶችም የኢኮኖሚ ማሻሻያው አካል መሆናቸውን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ሀገሪቱ ከእነዚህ ዘርፎች በርካታ ቢሊየን ዶላሮችን እያገኘች መሆኑን አመልክተዋል።
የተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች በየበኩላቸው እያበረከቱት ባለው ሁለንተናዊ ድርሻ ምክንያት የሀገሪቱ ኢኮኖሚ በተከታታይ እያደገ መሆኑን ገልጸው፤ በተያዘው በጀት ዓመት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የ 10 ነጥብ 2 በመቶ እድገት ያስመዘግባል ተብሎ እንደሚጠበቅ አስታውቀዋል።
የቱሪዝም ዘርፍን በተመለከተ በዘንድሮው ዓመት ከ1 ነጥብ 4 ሚሊየን በላይ የውጭ ሀገር ጎብኚዎች ኢትዮጵያን የጎበኙ ሲሆን፤ ይህም ቁጥር ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከ100 ሺህ በላይ፣ ከካቻምናው አንጻር ደግሞ የ300 ሺህ የጎብኚዎች ጭማሪ ማሳየቱን አብራርተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም የውጭ ቱሪስት ፍሰቱና የተገኘው ገቢ እያደገ ቢሆንም፤ ገና የሚፈለገው ደረጃ ላይ ባይደርስም የታየው ለውጥ ግን እጅግ ተስፋ ሰጪና በግልጽ የሚታይ መሆኑን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የኮንፈረንስ ቱሪዝም ማዕከል በመሆኗ በበጀት ዓመቱ 204 ዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶችን እና ታላላቅ ሁነቶችን ማስተናገዷን ገልጸው፤ ይህም ሀገሪቱ በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተሰሚነት ከማሳደጉም በላይ የኮንፈረንስ ቱሪዝም ስበት ማዕከል እየሆነች መምጣቷን ማረጋገጫ ነው ብለዋል።
በሰው ኃይል ልማት፣ በቱሪስቶች ፍሰት፣ በገቢ አሰባሰብ እና በአዋጪነት ረገድ የቱሪዝም ዘርፍ ለመንግስት የሪፎርም ስራዎች ፈጣንና አዎንታዊ ምላሽ እየሰጠ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አመልክተዋል።
በተለያዩ ጊዜያት ያጋጠሙ ፈተናዎች ቢኖሩም፤ ቱሪዝም ለብሄራዊ ኢኮኖሚው ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝና ዘርፉን እንደ አንዱ የኢኮኖሚ ምሰሶ አድርጎ መምረጥና መዋዕለ ንዋይ ማፍሰሱ ፍጹም ትክክለኛ እርምጃ እንደነበር በተከናወኑት ስኬታማ ስራዎች ማረጋገጥ ተችሏል ብለዋል።
01/07/2026
የታሪካዊ ቅርሶች ዕድሳት የቱሪዝም ዘርፉን ለማሳደግና የሀገርን ገጽታ ለመቀየር ያለመ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
የኢትዮጵያ መንግሥት በተለያዩ አካባቢዎች እያከናወናቸው ያሉ የቤተ-መንግሥታት ዕድሳትና የቱሪስት መዳረሻዎች የማልማት ተግባራት ቅርሶችን ከመጠበቅ ባለፈ፣ የቱሪዝም ዘርፉን የኢኮኖሚ ሞተር ለማድረግ ያለሙ መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን የተናገሩት ከኤን.ቢ.ሲ ኢትዮጵያ ጋር "አዲሱ የኢኮኖሚ ሞተር" በሚል ርዕስ በቱሪዝም ዘርፍ ዙሪያ ባደረጉት ልዩ ቆይታ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው የተከናወኑ የቱሪዝም ልማት ፍሬዎች መንግሥት ቅርሶችን ጠባቂ፣ አሻጋሪና አዳሽ እንጂ አፍራሽ አለመሆኑን በተግባር ያረጋገጡ ናቸው ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከ35 በላይ በተለያዩ ዘመናት ከኢትዮጵያ የተወሰዱና የተዘረፉ ቅርሶችን ማስመለስ መቻሉን ተናግረዋል።
ቅርሶችን የምናስመልስና የምንጠብቅ እንጂ የምናፈርስ አይደለንም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ታሪካዊ ቦታዎች ላይ የተከናወኑት የዕድሳት ሥራዎች የቅርሶቹን ይዘትና ደህንነት በከፍተኛ ጥንቃቄ የጠበቁ መሆናቸውን አስረድተዋል።
ለአብነትም የጎንደር ፋሲለደስ ግንብ ለመቶ ዓመታት ያህል ሳይታደስ በቁሙ እየፈረሰና ግቢውም አሳዛኝ ሁኔታ ላይ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ላይ የተከናወነው ዘመናዊና ጥንቃቄ የተሞላበት ዕድሳት ለሚቀጥሉት 50 እና 60 ዓመታት ለትውልድ የሚሻገር እና ማንኛውም ጎብኝ የሚኮራበት መሆኑን ገልጸዋል።
የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ዕድሳት በውጭ ሀገር ባለሙያዎች አማካኝነት ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ እየተከናወነ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
ቀደም ሲል በመሠረተ-ልማት እጥረትና በተለያዩ ምክንያቶች ለመግባት አስቸጋሪ የነበረው የሶፍ ኡመር ዋሻ አሁን ላይ ከፍተኛ ለውጥ ተደርጎበት ለጎብኝዎች ምቹ መደረጉን ጠቁመዋል።
የጀጎል ግንብም ታሪካዊ ይዘቱን በጠበቀ መልኩ ውብ ሆኖ መታደሱን አንስተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ብሔራዊ ቤተ-መንግሥት ቀደም ሲል ግቢው ያረጁ ተሽከርካሪዎችና መሣሪያዎች የተሰበሰቡበት እንዲሁም የመሬት ውስጥ ክፍሉ በጎርፍ የተሞላና ለአያያዝ አስፈሪ የነበረ መሆኑን አስታውሰው፤ አሁን ላይ በሚሊየን የሚቆጠር ሕዝብ የሚጎበኘውና የሚኮራበት ስፍራ ሆኗል ብለዋል።
የቤተ መንግሥት ተሽከርካሪዎችን አድሶ ሥራ ላይ ማዋል ከፍተኛ ጥረት መጠየቁን አንስተው፤ ይሄንን እውነታ ወደ ጎን በመተው ቅርስ ተበላሸ የሚሉ ሀሳቦች በተጨባጭ መረጃ ላይ ያልተመሠረቱ ናቸው ብለዋል።
መንግሥት በቱሪዝም መዳረሻዎች ልማት ላይ የተከተለው መርህ ጥራትን እና ትክክለኛነትን መሠረት ያደረገ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አጽንኦት ሰጥተዋል።
በሀገሪቷ የሚገነቡትና የሚታደሱት መዳረሻዎች ሁሉንም ሃይማኖቶች፣ ሁሉንም አካባቢዎችና ታሪኮች በእኩልነት የሚያንጸባርቁና የኢትዮጵያን አጠቃላይ መልክ በአንድነት የሚያሳዩ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በሀገር ውስጥና በውጭ ባለሙያዎች የሚከናወኑት የልማት ሥራዎች በከፍተኛ የአመራር ክትትልና ትኩረት የሚመሩ በመሆናቸው የዕድሳትና ግንባታ ሂደታቸው ጥራቱን የጠበቀ መሆኑን አስገንዝበዋል።
በቱሪዝም ዘርፍ የተከናወኑት ሥራዎች ኢትዮጵያ ለዓለምና ለዜጎቿ የምታሳያቸውን ድንቅ ሀብቶች የገለጡ መሆናቸውን በማንሳት የተመዘገበው ውጤት እጅግ የሚያስደስት መሆኑን አመልክተው፤ መንግሥት የቅርሶች “አስዋቢና ዓይን ገላጭ” መሆኑን በተግባር ማሳየቱን ተናግረዋል።
01/07/2026
የጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ «መደመር» መጽሐፍ በቻይንኛ ተትርጉሞ፤ በቅርቡ ለንባብ ይበቃል!
በ2010 ዓ.ም የነበረውን ሀገራዊ ለውጥ ተከትሎ የኢትዮጵያ የነገ ጉዞ ፍኖተ-ካርታ ሆኖ የተወለደውና በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የተጻፈው የ«መደመር» መጽሐፍ፣ ኦፊሴላዊ የቻይንኛ ቋንቋ ትርጉም ሥራው በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል፤ በቅርቡም ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለንባብ ሊበቃ መሆኑ ተረጋገጧል።
ባለፉት አሥርት ዓመታት ከአፍሪካ አህጉር ፈልቀው ወደ ዓለም መድረክ ከተሻገሩ ጥቂት አገር በቀል ፍልስፍናዎች መካከል ግንባር ቀደሙ የሆነው «መደመር»፣ አሁን ላይ ተደራሽነቱና ይህን የኢትዮጵያ አገር በቀል የሆነው የመደመር ፍልስፍና በርካቶች በትኩረት የሚመለከቱት አጀንዳ እየሆነ ነው። ቻይና የትርጉም ሥራውን እያጠናቀቀች ባለችበት በዚህ ወቅት፣ መጽሐፉ ከዚህ ቀደም በአማርኛ፣ በአፋን ኦሮሞ እና በእንግሊዝኛ ካለው ተደራሽነት በተጨማሪ በቅርቡ በአረብኛ እና በፓኪስታን የኡርዱ ቋንቋዎች ተተርጉሞ በደማቅ ሁኔታ መመረቁ ይታወሳል። አሁን ደግሞ በቢሊዮኖች የሚነገርለትን የቻይናን መድረክ በይፋ ለመቀላቀል የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ይገኛል።
ይህ የ«መደመር» መጽሐፍ ወደ ቻይንኛ ቋንቋ መተርጎም እና አሁን ላይ ሀያል ከሆኑ አገራ መካከል የምትጠቀሰውን ቻይናን ትኩረት ማግኘቱ ከመጽሃፍ ትርጉም ሥራ ባለፈ በርካታ ስትራቴጂካዊ እና ፖለቲካዊ እንድምታዎችን ይዟል፡፡ እንደ ቻይና ዓይነት እጅግ የዳበረ፣ የረጅም ዘመን የፖለቲካ ፍልስፍና ታሪክ ያላት እና ከማኦ ዜዱንግ እስከ ዴንግ ዚያኦፒንግ፣ አሁን ደግሞ እስከ ፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ የዘለቀ የራሷ የርዕዮተ-ዓለም መስመር ያላት ሀገር፣ "መደመር"ን ኦፊሴላዊ በሆነ መንገድ ወደ ራሷ ቋንቋ መተርጎሟ፤ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ተጽዕኖ ፈጣሪና ትኩረት ሳቢ ፍልስፍና ማበርከት መቻሏን ማረጋገጫ ነው ። ኢትዮጵያ ባለፉት ዘመናት ከውጭ የሚመጡ ርዕዮተ-ዓለሞችን (Capitalism/Socialism) ስታስተናግድ የኖረችበትን የታሪክ ምዕራፍ በመቀየር፣ አሁን ግን የራሷን አገር በቀል ፍልስፍና ወደ ውጭ የምትልክ ሀገር ለመሆኗ ትልቅ ማሳያ ነው መደመር መጽሃፍ ።
መጽሐፉ አፍሪካን፣ መካከለኛው ምስራቅን (በአረብኛ)፣ ደቡብ እስያን (በኡርዱ) እና አሁን ደግሞ ምስራቅ እስያን (በቻይንኛ) ተደራሽ ማድረጉ፣ ፍልስፍናው ከተወለደበት የኢትዮጵያ ምድር ተሻግሮ አህጉራትንና የተለያዩ ባህሎችን የማስተሳሰርና የማቀራረብ ትልቅ የዲፕሎማሲ አቅም እንዳለውም ማሳያ ነው ።
የመደመር መጸሃፍ የቻይንኛ ትርጉም በቅርቡ ይጠብቁ!
01/07/2026
30/06/2026
ኤጀንሲው ሁሉንም የኩነት ምዝገባ በዲጂታል አሰራር እያከናወነ ነው -አቶ ሳዳም መሀመድ
ሁሉንም የኩነት ምዝገባዎች ሙሉ በሙሉ በዲጂታል አሰራር እያከናወነ እንደሚገኝ የሀረሪ ክልል ወሳኝ ኩነትና ምዝገባ ኤጀንሲ ሀላፊ አቶ ሳዳም መሀመድ ገለፁ።
ሀላፊው እንደገለፁት ኤጀንሲው በሁሉም ወረዳዎችና የጤና ተቋማት የዲጂታል የኩነች ምዝገባዎችን ተግባራዊ ማድረግ ተችሏል።
በ2018 በጀት ዓመትም ባጠቃላይ ከ 15 ሺ በላይ ኩነቶች የዲጂታል ምዝገባ ማከናወን መቻሉን ጠቁመዋል።
ኤጀንሲው ከወረዳዎች በተጨማሪ
በጤና ተቋማት የልደትና ሞት ምዝገባን በአንድ ማዕከል እያከናወነ እንደሚገኝም አክለዋል።
ምዝገባው ሙሉ በሙሉ በዲጂታል የተደገፈ መሆኑ የተጣራ የጤናና ሌሎች መረጃዎችን ለማግኘት ያስችላልም ብለዋል፡፡
ኤጀንሲው ከ 2015 በፊት የተመዘገቡ የነዋሪዎችን መረጃ በዘመናዊ መንገድ ለማደራጀት ወደ ዲጂታል የመቀየር ስራ እየሰራ እንደሚገኝም አክለዋል።
በአገር አቀፍ ደረጃ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ን እውን ለማድረግ ፖሊሲ ተቀርፆ ወደ ስራ መገባቱን የገለፁት ሀላፊው ኤጀንሲው እያከናወነው የሚገኘው መረጃዎችን ወደ ዘመናዊ ስርዓት የማስገባት ተግባር ለሌሎች ስራዎች መሰረት የሚጥል ነው።
በተለይ የነዋሪዎችን መረጃ በዲጂታላይዜሽን መንገድ በማደራጀት ሌብነትንና ብልሹ አሰራርን ለመቅረፍ ሁነኛ ሚና አለው ሲሉ ገልፀዋል።
የወሳኝ ኩነት ምዝገባዎች ለሕጋዊ፣ለአስተዳደራዊና ለስታትስቲክስ ዓላማዎች ጥቅም ላይ እንደሚውሉም አስገንዝበዋል ።
በተለይ በአንድ አገር በዜጎች ከልደት እስከ ህልፈተ-ህይወት የሚከሰቱ ወሳኝ ኩነቶች ማለትም እንደ ልደት፣ ጋብቻ፣ ፍቺ እና ሞት ያሉ ክስተቶች የአንድን አገር ቀጣይ የልማት አቅጣጫ የመወሰን አቅም ያላቸው መሆኑን ጠቁመዋል።
ኤጀንሲው ቅንጅታዊ አሰራሩን በማጎልበት በጤና ተቋማት የኩነት ምዝገባ አገልግሎትን ለማስፋት እየሰራ በመሆኑ ዜጎችም እያንዳንዱን ኩነት በወቅቱ በማስመዝገብ የዜግነት ግዴታቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል።
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Website
Address
Dire
Addis Ababa
