Yadesa Hassen Adme
Education
27/09/2022
የዌራ ወረዳ ት/ጽ/ቤት በአድሱ ስርዓተ ትምህርት ሙሉ ለሙሉ ለመተግበር የመምህራን ስልጠና እና የመጽሐፍት ህትመት ስራዎችን ጨምሮ የተለያዩ ዝግጅቶች እየተደረገ መሆኑን አስተውቀዋል ።
በሀላባ ዞን የዌራ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት በአድሱ ስርዓተ ትምህርት ሙሉ ለሙሉ ለመተግበር የመምህራን ስልጠና እና የመጽሐፍት ህትመት ስራዎችን ጨምሮ የተላያዩ ዝግጅቶች እየተደረገ መሆኑን የዌራ ወረዳ ት/ጽ/ቤት ዋና ሀላፊ አቶ ያድሶ ዱበላ ገልፀዋል ።
ዋና ሀላፊው በአድሱ ስርዓተ ትምህርት ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ በወረዳው እየተደረጉ ያሉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተስፋ ሰጪ ውጤቶች የታየባቸው በመሆኑ ከ2015 ዓ.ምን ጀምሮ ስርዓተ ትምህርቱ በሁሉም ዌራ ወረዳ ባሉ ት/ቤቶች ተግባራዊ እንደሚደረግም ገልፀዋል ።
በዘንድሮ አመት ስርዓተ ትምህርቱ ሙሉ ለሙሉ መተግበር ከጀመረ በኃላ ሁሉም ት/ቤቶች የመማር ማስተማር ስራው እንዳይስተጓጎል ከወዲሁ አስፈላጊ ግብዓቶችን የማሟላት ስራ ትኩረት እንዲሰጠውም ጠይቀዋል ።
የዌራ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት!!
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Website
Address
Halab
